በድንቁርና ውስጥ ሀገሪቱ ትገኛለች ሲባል ይህን ምርምር ከአደረግሁ በኋላ በደንብ ግልጽ አለልኝ። ለምሳሌ ከመደናቆራችን ጥልቅነት ዋናውን ሀብት አለመለየትና በዚያ ዙሪያ ትውልድን መገንባት አለምቻል ለብዙ ችግሮች ዳርጓል እየዳረገም ይገኛል። በወተት፣ በሥጋ፣ በአትክልት፣ ወዘተ ምርቶች ሀገሪቱ መትረፍረፍ ነበረባት። ምክንያቱም ሀገሪቱ በዝናብ ውኃ ሀብት ጥገኛ እንደመሆኗ መጠን በዝናብ ውኃ ሀብት ዙሪያ ት/ቤቶች መጽሐፍ የላቸውም ቢባል ማጋነን አይሆንም። ስለዚህ በትክክለኛው ጎዳና ሀገሪቱ አይደለችም ይህም የድንቁርና ውጤት ነው ማለት ይቻላል።
ከዚህ ችግር ለመውጣት ይህ ፕሮግራም ከልብ ተይዞ በመተግበሩ ለኢትዮጵያ ያቀድነው ለዓለምም ተርፎ እስካሁን ያልተገለጸውን ዝናብንና ሥነ-ምህዳርን የሚያስተዳድረውን የመሬትን ንድፍ ማብሰር ችለናል። ይህ ንድፍ የተለያዩ በሰው አቅም ሊተገበሩ የማይችሉ ትግባራትን ይፈጽማል።
ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላችሁ።
ይህ ሂደት በብዙ ዘርፉ ጠቃሚ ሲሆን የሚያደርጉት ድጋፍ ከልጆች ዕውቀት ከማዳበር ጀምሮ የሥራ ዕድል በመክፈትና ልማትን በማስፋፋት ሀገር የሚጠቅም መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ለሀገር መሠረት በመጣል ሁሉንም በማስተባበር ወደየት መጓዝ እንዳለብን ብቸኛውን አቅጣጭና መንገድ ይዞ ብቅ ብሏል። በማንበብ ወደፊት ለምናደርገው ውይይትና የልማት አቅጣጫ ተሳታፊ ይሁኑ በማለት ልንጋብዝዎ እንወዳለን።
መጽሀፎች ለዚህ ንድፍ መገኘት ብቸኛ ምክንያት ናቸው። ጽሀፊው የዓለምን ንድፍ የደረሰበት የመጀመሪያ 4 መጽሀፎችን በመጻፉ ነው። ስለዚህ ታሪካዊ ያደርጋቸዋል። እያንዳንዱ መጽሐፍ ቁምነገር እንዳለው ተገንዝበው በእጅዎ ወይም ለልጅዎ ለማቅረብ ከፍተኛ ጥረት ያድርጉ። ሁሌም ይመራመሩበታል። ይረኩበታል! ምክንያቱም ከህይወት ጋር የተቆራኘ ስለሆነ ከሂደቱ መራቅ አንችልም ስለዚህ በዚህ ዙሪያ ዕውቀት ማካበት ለወደፊት እንጀራ መጋገር ማለት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ይህን ችላ ማለታችን ዋጋ እያስከፈለን ይገኛል። መልማት የሚችል አካባቢ ተይዞ መራብና ለልመና መዳረግ አይገባም ነበር።
ይህን በመቀየር በውጤት ታሪክ ይስሩ፤ አብረዎን ይጓዙ!